Menen Daniel

Menen Daniel Model and actors

መልካም ፋሲካ  ✝️💒🙏
12/04/2026

መልካም ፋሲካ ✝️💒🙏

ሞተች👸✍️✍️ ✍️ሞተች እኮ እሷ፤የምድር ቆይታን በጊዜ ጨርሳአንድም ቀን ሳታርፍ ሳትደሰት ነፍሷሞተች እኮ እሷ ፤ያኔ ሰትደክም ነግራው ነበር ለእግዜርአሳረፋት ቃሏን ሰምቶ ይብቃሽ ቢላት ነበር...
31/03/2026

ሞተች👸✍️✍️ ✍️
ሞተች እኮ እሷ፤
የምድር ቆይታን በጊዜ ጨርሳ
አንድም ቀን ሳታርፍ ሳትደሰት ነፍሷ
ሞተች እኮ እሷ ፤
ያኔ ሰትደክም ነግራው ነበር ለእግዜር
አሳረፋት ቃሏን ሰምቶ ይብቃሽ ቢላት ነበር
እሷ ፣ ሀሳቧ እረጅም የቆመችው በአጭር
እግዜር፣ ረጅም ብትሄድ መሰበሯን ያውቅ ነበር
እሷ ፣ ያልተሳካው ረጅም ጉዞ ሆኖ ነበር የሷ ህመም
እግዜር ፣ ልብ ሰጣት ያሰበችው ለስጋ እንጂ ለነፍስ?
ተመለሰች ልብ ገዛች ከአለም ኑሮ ከትግሉ፣
ገለል አለች ለነፍስ ስንቋን ልታበጃጅ፣
ግና ሰው አይደለች የሰጋ ፆር ቢበረታ
ተመለሰች ለአለም ትግል ልትበረታ፣
ግን አልሆነም እዛው መርገጥ እዛው መውደቅ፣
ሆነና አደከማት በድጋሚ ሳትመለስ ወደነፍሷ
እሷ፤ ሞተች እኮ 👸
ላይለቀስ ሙሾ ላይወርድ፣
ሳይጠራ ልጅ በስሟ
እሷ፣ ለነፍሷ ሳትበቃ ወይ ለስጋዋ
እንዲሁ ሞተች ሰማን እኛም
ከንፈር ልንመጥ ልናዝንላት
አሁን፣ ሞተች እኮ እሷ።
ተስፋ የነገ ብርሀንን እንድናይ ያደርገናል።
የብርሀን አምላክን መያዝ በቃሉ መመላለስ የለመለመ ነገን የእኛ እንዲሆን ያደርገናል።እግዚአብሔር ይመስገንን ✝️✝️✝️💒💒💒🙏🙏🙏

...........................✍️✍️✍️✍️

✍️ ✍️✍️ ፀሀፊ መነን ዳንኤል👸🦋

ከጠብታ ታሪክ።

ሰላም የተወደዳችሁ እንዴት ከረማቹ ።ዛሬ አዲስ ታሪክ አለኝ እነሆ ለእናንተ።     ✍️✍️✍️ የዛሬ ባለ ታሪካችን ከወደ ደቡብ ለምለሚቷ አካባቢ ተወልዳ ያደገች  ስለ አንዲት ወጣት ታሪክ ነ...
28/03/2026

ሰላም የተወደዳችሁ እንዴት ከረማቹ ።ዛሬ አዲስ ታሪክ አለኝ እነሆ ለእናንተ።
✍️✍️✍️ የዛሬ ባለ ታሪካችን ከወደ ደቡብ ለምለሚቷ አካባቢ ተወልዳ ያደገች ስለ አንዲት ወጣት ታሪክ ነው የማካፍላቹ። አንዲህ ትለናለች ፦እድሜዬ በ20ዎቹ ውስጥ እገኛለሁ ተመርቄ ሰራ ከጀመርኩ ጥቂት አመታትን አስቆጥሪያለሁ እራሴን ጠንካራ ሴት ነኝ ባልልም ሁሉም ሰው ጠንካራ እና ብርቱ ሴት መሆኔን ይነግረኛል። በእርግጥ ድክመቴን በሰዎች ፊት አላሳይም ሰዎች ከእኔ እንዲያዩት የምፈልገው ጥንካሬዬን ብቻ ነው። የእኔን ደካማነት የሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ውጭ ላይ ቢከፋኝም ብደሰትም ተመሳሳይ ነው ሳቄን ብቻ ነው የማሳየው እቤቴ ስገባ እና ቤተክርስቲያን ስሄድ ትክክለኛዋን እኔን አገኛለሁ በአምላኬ ፊት ደካማ ነኝ ያውቀኛል። አይገምተኝም አለቃቀሴን አይቶ አያሳፍረኝም አይወቅሰኝም ብቻ በዝምታ መረጋጋትን ፣መፅናናትን ዕረፍትን፣ ይሰጠኛል። እኔ ጎበዝ አማኝ ባልሆንም ሁልጊዜ መሸሸጊያዬ እግዚአብሔር ነው መጠጊያዬ ነው። እንደዚህ ነው ከአምላኬ ጋር የኖርነው። ሁሌም በህይወቴ አዳዲስ ነገር እንዲኖር እፈልጋለሁ።ሁልጊዜ የተደጋገመ ህይወት ይሰለቻል ስለዚህ አጥብቄ አምላኬን ጠየቅኩት። መልስ ይሁን አይሁን አላውቅም እንደተለመደው ብቻ ሆነ አዲስ ነገርም ለመቀበል ሞከርኩ በዙሪያዬ ለትዳር የሚጠይቁኝ ሰዎች ነበሩ የመጡት ሰዎች ሁሉ በዕድሜ ይበልጡኛል በማስተዋል ግን እጅጉን እንራራቃለን የትኛቸውም ለእኔ የሚሆኑ መስለው አልታዩኝም። ሁሉንም ወደ እኔ የሚመጡ ፈላጊዎችን ዘጋሁ።አሁን ለእራሴ አልኩ ይህውልሽ ምንም ነገር ጊዜ አለው ፀልየሽ ነገርሽን ለእግዚአብሔር ሰጥተሽ እረፊ ብዬ አጭር ትዕዛዝን ለራሴ አስተላለፍኩ። በዛ መንገድ ሀሳቤን ለእግዚአብሔር ሰጥቼ ኑሮዬን ቀጠልኩ። ከእለታት በአንዱ ቀን ማህበራዊ ድረ ገፅ ስከፍት የመልዕክት ማስቀመጫ ላይ አንድ መልዕክት ተመለከትኩ። ብዙም በዛ የሚላኩ መልዕክት ባልከፍትም እንደአጋጣሚ ሆኖ ይሄን መልዕክት ከፈትኩ። መልስ ሰጠሁ እንግዲህ እንዲ የተጀመረ መልዕክት ሳይቋረጥ ለአንድ አመት ከስድስት ወር ቀጠለ በአካል ተገናኝተን አይቼው አይቶኝ አያውቅም። እኔ የዘጋሁትን ፋይል መክፈቴ ይሄ ሰው በህይወቴ ካየኋቸውም ካጋጠሙኝም ሰዎች የተለየ ሰው ነበር። በመጀመሪያ የተማረኩት በጭንቅላቱ ነበር በጣም ድንቅ አስተሳሰብ አለው በሳል ነው ሴትን ልጅ የሚያከብር ፣ የወንድነት ፀጋን የተላበሰ፣ ብቻ የትኛዋም በሳል ሴት የምትፈልገው አይነት ወንድ ነው። ተገረምኩ እንደው እግዚአብሔር ድንቅ አደረገ እኔ ሁሉን ስተው እሱ ስራውን ሰራልኝ ብዬ ለሀገር ለምድሩ ተናገርኩ የእኔ ደስታን የሚጠባበቁ ሁሉ ከእኔ በላይ ተደሰቱ። በፍጥነት እንድንጋባ እፈልጋለሁ አለኝ። ደነገጥኩ እንዴት ይሆናል ብዙ ማድረግ ያለብን ነገር አለ አልኩት ምን አለ አለኝ በመጀመሪያ እኔ እና አንተ በአከካል ተገናኝተን መተዋወቅ ማውራት መግባባት አለብን ቀጥለን ጉዳያችንን ወደ ቤተሰብ እንወስዳለን በመጨረሻም ወደ ቤተክርስቲያን ሄደን ጋብቻ እንፈፅማለን አልኩት። አልተቃወመኝም እንደ ቃልሽ ይሁን አለኝ። ቀጠልን እያወራን ሶስት ወራት አለፉ ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም። ጠየቅኩት ለመቼ አሰብክ አልኩት በቅርቡ አለኝ በመሀል እኔ ስራ አቆምኩ ሁሉ ነገር አስጠላኝ። ከእሱ ጋር ግን ይሄ የማይባል የደስታ ምንጬ ሆነ። ስራ ሳቆም ወጭዎቼን መሸፈን ስለነበረብኝ አለመስራትም ስለማልችል ስራ ፍለጋ እወጣለሁ እወርዳለሁ ያው በዚህ ጊዜ ስራ ማግኘት ከባድ ነው። ከተወሰኑ ጊዜያት በኋላ ስራ አገኘሁፈ ህይወት
ቀጠለ ጊዜያት ነጎዱ በቅርብ ያለኝ አመት አለፈ። ከወሬ ውጭ ያ በእኔ ጭንቅላት ውስጥ ያለው ፀጋ ያለው ቤተሰቡን የሚንከባከብ አጠገቡ ላሉ ከለላ ብዬ ያን ሁሉ ሰዕል እውነት እንዳልነበር ገብቶኛል ግን ወድጄው ስለነበር ሁሉንም ነገር ተቀበልኩት። አሁን እንዳሉ እኩዮቼ በዚህ ቀን እንዲ ሆነ ፍቅረኛዬ እንዲህ አደረገልኝ የፍቅረኛሞች ቀን ወይም ሌሎች በዓላት ታውሰው አያውቁም። እኔም አልጠብቅም እኔ ላድርግ ብል እንኳን አልችልም። በመጨረሻም ክብሬንም ፍቅሬንም እምነቴንም አጠፋው። እንደ ሴት የሚገባኝን ሁሉ ከመከልከሉ ያለኝንም ለመንጠቅ ሞከረ። ያን ሁሉ ጊዜ ከንቱ ነበር አንዳንዴ የሚሰማንን ብናዳምጥ ከብዙ ጥፋት እንድን ነበር። ለዛን ሁሉ ጊዜ አስጠብቆኝ በመጨረሻ ጠፋ መፃፍ አቆመ እኔም መልዕክቶችን ልኬ ነበር አይመልስም። እኔ ሁሉንም ነገር ባውቅም በጣም ተጎዳሁ ወራት አለፉ።ከወራት በኋላ በቤተሰብ በኩል ሰው እንድተዋወቅ ተደረኩ ተዋወቅን እንደ ሴት የማፈቅረውን ሳይሆን የሚያከብረኝን የሚያፈቅረኝን ማን እንደሆንኩ ቤተሰብን የሚያውቀውን ያየሁትን ተቀበልኩ። ጊዜ አልወሰደም ሽማግሌ ልኮ በቤተክርስቲያን ስርዐት ተጋባን።ከወራት በኋላ የአራት ወር እርጉዝ ሆኜ ይሄን የረሳሁት የተውኩት ሰው መጣ። ካድሽኝ ዋሸሽኝ ብሎ ብዙ የንግግር ናዳ አወረደብኝ። ይሄን ባለቤቴ አወቀ ጠየቀኝ ነገርኩት ከዛም በፊት ሁሉንም ነገር ነግሬዋለሁ ግን በአዲስ እኔን መውቀስ ጀመረ። ያኛውም እኔን ይወቅሳል ባለቤቴም እኔን ወቃሽ ሆነ። እኔ በመሀል ቤት እውነቴን የማስረዳው ሰው አጣሁ። ማነው ትክክል፣ ማነው የተሳሳተው? ግራ ገብቶኛል። ትለናለች ይሄ ህይወት እንዴት እንደሆነ ባላውቅም እስኪ ምከሩኝ ትላለች። እናቶች ሁሌም ለሴት ልጃቸው ከመልክሽ እድልሽ ይመር ብለው መመረቃቸው ሀቅ ነው።ሰውን ቃሉን ይጠብቃል ያለውን ያደርጋል ማለት በአሁን ጊዜ ከባድ ነው ባይሆን ስድስተኛ ህዋስን ቀልብን ማዳመጥ እና እግዚአብሔር መጠየቅ መልካም ነው። ቅን ልብን መልካም የሚያስብ አዕምሮን ይፍጠርልን። በምድር እንግዶች ነን አይደለም ለክፋት ለፍቅርም የሚሆን ረጅም እድሜ የለንም።በዚህ አጭር እድሜ ዋሽተንበት፣ በድለንበት ገድለንበት። አይበቃንም ለመፋቀር እንጠቀመው። እህቴ ፍቅር የሚኖር ነው የሚወራ አይደለም። ቀድሞውኑ የአንቺ ሰው ቢሆን ለዛን ሁሉ ጊዜ አያስጠብቅሽም ምክንያት ቢኖረው እንኳ በምትረጅው መልኩ ያስረዳሻል ብቻ በእውነት ፍቅር ያለው ወንድ ከቃሉ ተግባሩ ይበልጣል። ያኛውን ይለፍሽ ትዳርሽን አጥብቂ። በመካከላቹ እግዚአብሔርን አፅኑ ፀልዩ። እርሱ መልካሙን ያደርጋል። ወንድሞቼ ብትችሉ የማትፈልጓትን ሴት አታቆዩ ሴት አበባ ናት ። ለሁላችንም የማይሻር መልካም ፍቅር እግዚአብሔር በልባችን ያፅና።አሜን

ፀሀፊ ፦ መነን ዳንኤል ✍️✍️✍️

ባለታሪካችን እናመሰግናለን

✍️✍️ ሰላም ተወዳጆች part 4 እንዳዘገየሁት አውቃለሁ ለዛም ከልብ የመነጨ ይቅርታን እጠይቃለሁ። እነሆ አሁን ተለቋል [  ] part 4   ✍️✍️ ቀና ስል ያየሁትን ማመን አቃተኝ፤ ስለ...
13/03/2026

✍️✍️ ሰላም ተወዳጆች part 4 እንዳዘገየሁት አውቃለሁ ለዛም ከልብ የመነጨ ይቅርታን እጠይቃለሁ። እነሆ አሁን ተለቋል

[ ] part 4 ✍️✍️ ቀና ስል ያየሁትን ማመን አቃተኝ፤ ስለ አለቃዬ ላጫውታቹ አሁን ከፊት ለፊቴ ቆሞ ያየሁት ሰውነቴ በረዶ እስኪሆን በድንጋጤ ያቀዘቀዘኝ ሰው በአንድ ወቅት አፈቀርኩሽ በሚል ሰበብ መግቢያ መውጫ ያሳጣኝ ሰው ነበር እሱን ላለማግኘት ሰፈር ቀይሬያለሁ፣ ስልክ ቁጥር ቀይሪያለሁ፣ በቻልኩት መጠን በየትኛውም ማህበራዊ ገፆችም እንዳያገኘኝ ተከላክያለሁ። ለምን ጠላሽው ራቅሽው ልትሉ ትችላላቹ? የተዋወቅነው እኔ አንድ ድርጅት ላይ እሰራ ነበር በአጋጣሚ ይሄ ሰው ደምበኛችን ነበር ስራው ከውጭ የሚገቡ የተለያዩ መሳሪያዎችን ያከፋፍላል ጅርጅታችን እሱም የዚህ እቃዎች ተጠቃሚ ነበር። በዚህ የተጀመረ ትውውቅ ወደድኩሽ የሚል መልዕክት መጣ እኔም በጨዋ መልክ አለመፈለጌ ጥያቄውን አለመቀበሌን አስረግጬ ተናገርኩ። ለምን አለኝ መዋሸት አልፈለኩም ስለዚህ ትክክለኛውን መልስ ተናገርኩ። አልፈልግም ምክንያቴ የምፈልገው ነገር እሱ ጋር የለም ። ምንድነው የምትፈልጊው? በተግባባንባቸው ጊዜያት ትንሽም ቢሆን የታየኝ ማንነት አለ ያን ደሞ እኔ አልወደውም። እኔ የምፈልገው ስብዕና ማየት አልቻልኩም ስለዚህ አንተን መቀበል አልችልም አልኩት። እሱ ግን እልህ ያዘው ጠዋትም ማታም መሄጃዬን አጣበበብኝ። ስራውን ተውኩት ከላይ እንደተናገርኩት በየትኛውም መንገድ እሱ እኔን ማግኘት እንዳይችል መንገድ ዘጋሁ ከዛ በኋላ ነበር ስራ ፍለጋ ስወጣ እሱ ድርጅት ውስጥ የተገኘሁት። በዝምታ ተዋጥን ሁለታችንም ደንግጠናል። ወደራሴ ተመልስኩ እና ዞር ብዬ ቦርሳዬን ለማንሳትት ስዞር ምን ልታደርጊ ነው አለኝ? ልሄድ፤ ለምን? ትክክለኛ ቦታ አይደለሁም አልኩት። ቁጭ በይ እናውራ አለኝ። ስለምን? ስለ ሁሉም። እሺ ። ቁጭ አልኩ፣ እሱም ተቀመጠ። ለምን እንደዛ አደረግሽ ? ምን ማድረግ ነበረብኝ? ትክክል አልነበርሽም። እሺ። የእኔ መልስ ነበር አሁንም ከእሱ ጋር ማውራት አልፈለኩም። በረጅሙ እየተነፈሰ........ አሁን ይሄ ስራ ቦታ ነው ከእኔ እና ከአንቺ ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም ስራሽን መስራት ትችያለሽ። እኔ አለቃሽ ነኝ በቃ ሌላ ነገር የለም። ያ ያለፈ ታሪክ ነው። መልካም ቀን ብሎኝ ቢሮዬን ለቆልኝ ወጣ። ጭንቅላቴ ተጨነቀ ይበል እንጂ ያለፈ ታሪክ እንደማያደርገው እርግጠኛ ነበርኩ ስለዚህ የሱን ሀሳብ መስማት አልፈለኩም በድጋሚ ሌላ ስራ መፈለግ እንዳለብኝ ተሰማኝ። ስልኬን ከቦርሳ አውጥቼ ስመለከት መልዕክት አለኝ።እንግዳዬ ነበር የሱን መልዕክት ሳነብ ጭንቀቴ ሁሉ ወዴት እንደጠፋ አላውቅም ደስ አለኝ ለሱ መልዕክት መፃፍ ጀመርኩ ፅፌ ስጨርስ ከራሴጋር ለማውራት ሞከርኩ ስራ እስካገኝ መስራት እንዳለብኝ ወስኜ ወደ ስራ ገባሁ። ስራዬን እየሰራሁ ከእንግዳዬ ጋር በየመሀል መልዕክት እንላላካለን ምሳ ስዓት ደረሰ ወጥቴ በዛው ቡና እጠጣለሁ በዛው እበላለሁ ብዬ ቦርሳዬን ይዤ ለመውጣት ስንደረደር አለቃዬ መጣ። ምሳ እየወጣሽ ነው? አዎ፣ አብረን እንውጣ? አይ እታች ሰው እየጠበቀኝ ነው። እሺ መልካም ጊዜ አለኝ እና ሄደ አሁንም ምቾቴ ተነሳ፣ ወረድኩ እና ምሳ እቃ ከፍቶ ለብቻዬ መብላት አስጠላኝ። ግራ እየተጋባሁ አስተናጋጁዋ መጥታ ምን ልታዘዝ ስትለኝ፥ ውሀ አልኳት በዚህ ቅፅበት እንግዳዬ መልዕክት ላከልኝ፥ ለምሳ ወጣሽ አለኝ፤ አዎ እሩቅ ነው ስራ ቦታህ አልኩት? አይ አይደለም። የት ነው? ቦሌ ። እንዴ እኔም እኮ እዛው ነኝ። ለምን ምሳ አብረን አንበላም ብዬው ቦታዬን ነገርኩት። በሚገርም ፍጥነት መጣ ምሳችንን አብረን በላን ስራ ቦታዬን አየው። ከዛ እሱም ወደ ስራው ተመለሰ እኔም ወደ ስራ ገባሁ። አመሻሽ ስራዬን ጨርሼ ከስራ መውጫ ስዓት ደርሶ ልወጣ ቢሮዬን እየቆለፍኩ አለቃዬ መጣ። እየወጣሽ ነው? አዎ እየወጣሁ ነው። አሪፍ ወዴት ነሽ ላድርስሽ? አመሰግናለሁ ከሰው ጋር ነኝ። እሺ መልካም ምሽት ብሎኝ በፍጥነት ወደ ፊት ተራመደ። እኔም የቢሮዬን ቁልፍ በቦርሳዬ እየከተትኩ መራመድ ጀመርኩ። በስልኬ መልዕክት ገባ እንግዳዬ ነበር። በር ላይ ነኝ አልወጣሽም? በፍጥነት እየተራመድኩ እየመጣው ነው አልኩት። በር ላይ ቆሞ እየጠበቀኝ ነበር። አሁን ጉዞ ወደ ቤት ፊቴ ላይ ግን ትንሽ ጭንቀት አለ ገብቶታል ግን መጠየቅ አልፈለገም። አንድ ቦታ እንሂድ አለኝ? የት? እንጦጦ ኪዳነምህረት ተሳልመን እንምጣ አለኝ። ልቤ እንዴት በሀሴት እንደዘለለ። እሺ በጣም ደስ ይለኛል አልኩት። ጉዞ ወደ እንጦጦ ኪዳነምህረት። ነጠላ አልያዝኩም ነበር ሽሮ ሜዳ ነጠላ ገዝቶ ሰጠኝ ነጠላዬን ለብሼ ሄድን ስንደርስ ደስ የሚል አየር ቅዝቅዝ ያለ ንፋስ ብቻ ፀሎታችን ፀልየን ተቀመጥን ለረጅም ሰዓት። እንግዳዬ እንዲህ አለኝ ሲጨንቀኝ እዚህ መጥቼ ለእናቴ እነግራታለሁ እሷም ታስተካክልልኛለች። ንገሪያት የልብሽን ሁሉ እሷ የሁሉም እንባን ታብሳለች። ለሰው ቢነግሩት ትርፉ ወሬ ብቻ ነው ለእግዚአብሔር የነገሩት ግን መፍትሔ አለው እሺ። አለኝ አዎንታዬን አንገቴን በመነቅነቅ ገለፅኩለት። ብዙ እረፍትን ተሰማኝ። አመስግኜው አሁን እንሂድ አይደል እየጨለመ ነው አልኩት። እሺ እንሂድ ብሎኝ ተሳልመን መንገዳችንን ጀመርን። ወደ ቤት አድርሶኝ ተመለሰ እኔ ወደቤት ገብቼ ልብሴን እየቀየርኩ ብዙ ሀሳብ ማሰብ ጀመርኩ። አሁን ሌላ ስራ መፈለግ አለብኝ የአለቃዬ አካሄዱን አልወደድኩትም። እንግዳዬን ወድጄዋለሁ ለአፍታም ሀሳቤ ከእሱ እንዲርቅ አልፈልግም። አይኖቹ ውስጥ ያለው ርህራሄ፣ ለቤተክርስቲያን ያለው ቅርበት፣ ቅንነቱ፣ የዋህነቱ፣ ንፁ ልብ ያለው ሰው ነው። ይሄ ለእኔ የፀሎቴ መልስ ነው። እሱ በረከቴ ነው። ልቤ ይሄንን ያምናል። አሁን ምን ላድርግ ያለውን ነገር ለእንግዳዬ ነገሬው ስራ መፈለግ ላይ ያግዘኝ ወይስ እራሴ ልወጣው? አለቃዬ እንደማይፋታኝ አውቃለሁ። ስለ እንንግዳዬ ከሰማ ደሞ ለማጣላት እና ለማለያየት ቅድሚያ ተሰላፊ ነው። ለምንድነው ግን አንድ ጥሩ ነገር ሲመጣ መከራን ችግርን አስከትሎ የሚመጣው?

✍️................................

✍️✍️✍️ መነን ዳንኤል .............

✍️ 🦋እንዲህ የሳቅኩ እለት፦💔 ልቤ ተንከታክቷል🦵እግሬ መቆም አቅቶታል😥ከአይኔ እንባ ደርቋል🦋ነፍሴ መብረር አምሯታል አካሌ ከነፍሴ መግባባት አቅቶታል😂 እንዲህ የሳቅኩ እለት፦🚶‍♀️ አካሌ ዝ...
26/02/2026

✍️ 🦋እንዲህ የሳቅኩ እለት፦
💔 ልቤ ተንከታክቷል
🦵እግሬ መቆም አቅቶታል
😥ከአይኔ እንባ ደርቋል
🦋ነፍሴ መብረር አምሯታል
አካሌ ከነፍሴ መግባባት አቅቶታል
😂 እንዲህ የሳቅኩ እለት፦
🚶‍♀️ አካሌ ዝሏል
🙏ፀሎት ከቋቱ አልቋል
✝️ተስፋ ተሟጧል
💔ህይወት አብቅቷል
👸ጨንቅላት ለአክሊል
💔 ሳይሆን አንገት ለገመድ ተዘጋጅቿል
😥ጉሮሮ ለመርዝ ተስተካክሏል
💝ልብ ስራውን ሊያቆም ቋጠሮ ፈቷል
😂 እንዲህ የሳቅኩኝ አለት፦
አይደለም ሞልቶልኝ
ጎዶሎ ቢበዛ መሸፈኛዬ ነው
መናቅ መገፋቴን መከላከዬ እሱ ነው
ውርደት ነቀፋዬን ሰው እንዳያይብኝ
ጓዳ መከለያው
😂እንዲህ የሳቅኩኝ እለት፦
የሁሉንም ጥግ ደርሼ ስመለሰ?
መኖር ግዴታ መሆኑ ስረዳ አማራጭ የለኝም ከህይወት ጋር እየተናነቁ መኖርን እንቀጥላለን ምርጫው መኖር ብቻ ነው። የሆነው ሁሉ ይሁን ብቻ የሁሉም መልስ ከእርሱ ዘንድ ነው። ✝️🙏💒 ከማህደራችን የተገኘ። የብሶት ሙሾ ይላል።እንዲህ የሳቅኩኝ እለት አትመኑኝ የመከፋቴ ጥግ እንጂ የምቾቴ ማንፀባረቂያ አይደለም ትለናለች። ፅናት ለሁላችንም ይስጠን። 🙏

✍️✍️✍️ መነን ዳንኤል

part 3 ✍️✍️ የመጀመሪያዎቹን ገፆች ማንበብ እንዳትረሱ ይሄኛውን ከማንበባቹ በፊት።     ✍️✍️ ከቤተክርስቲያን ወደ ቤት ሸኝቶኝ እሱም ወደ ቤቱ እኔም ወደቤት ገባሁ። ገብቼ ልብሴን እ...
25/02/2026

part 3 ✍️✍️ የመጀመሪያዎቹን ገፆች ማንበብ እንዳትረሱ ይሄኛውን ከማንበባቹ በፊት።
✍️✍️ ከቤተክርስቲያን ወደ ቤት ሸኝቶኝ እሱም ወደ ቤቱ እኔም ወደቤት ገባሁ። ገብቼ ልብሴን እየቀየርኩ ሀሳቤን መሰብሰብ አልቻልኩም የቀየርኩትን ልብስ እንደነገሩ ወርውሬ ፍራሼ ላይ አረፍ አልኩ። ስልኬን አነሳሁ ስሙን ከስልኬ ላይ ከመዘገብኩ በኋላ ቴሌግራም ላይ ፎቶውን ለማየት ፈለኩት ፎቶ አላስቀመጠም። ስልኬን በእጄ እንደ ያዝኩ ከራሴ ጋር መጣላት ጀመርኩ። አንቺ ምን ሆነሻል በአንድ ቀን ሁሉም እንዳልነበር የምታደርጊው ጤነኛነሽ እራስሽን ተቆጣጠሪ የታየ ሁሉ አይገኝም የተሰማ ስሜት በሙሉ ልክ ነው ማለት አይደለም ተረጋጊ ለራሴ በቁጣ ተናገርኩ። ተነሺ ህይወትሽን ኑሪ አልኩ። ቁጣውን ልክ እንደሆነ ስለገባኝ ካለሁበት ተነሳሁ ነጠላዬን ማጣጠፍ ጀመርኩ ለብሼው የነበረውን ልብስ በአግባቡ አስቀመጥኩ። ከዚህ ሀሳብ ለመውጣት እራሴን በስራ መጥመድ ፈለኩ ሳስታውስ ነገ ወደ ስራ እገባለሁ ስለዚህ ለምሳዬ የሚሆን ምግብ ማብሰል አለብኝ። ቀጥይ ወደ ስራ ብዬ እራሴን ጀመርኩ። ለምሳ ምን ልያዝዝዝዝዝ ትዝ ሲለኝ ምስር አለ ምስር ወጥ ለመስራት ጉድ ጉድ ለማለት ስጀምር ከስልኬ የመልዕክት ድምፅ ሰማሁ 🙄 በአዕምሮዬ እሱ ስለነበር እያሰብኩ የነበረው ሌላ መልዕክት ባይሆን እየተመኘሁ ወደ ስልኬ አመራሁ ከፈትኩት ቴሌ ነው ደሜ ተንተክትኮ መልዕክቱን አጥፍቼው ወደ ስራ ተመለስኩ። ሽንኩርት እያቁላላሁ ምስሬን ማጠብ ስጀምር በድጋሚ የመልዕክት ድምፅ ሰማሁ። በድጋሚ ቴሌ እንደሚሆን ገምቼ ሰራዬን ቀጠልኩ ግን አዕምሮዬ የስልኩ መልዕክት ላይ ነው። ምስሩን ማጠቡን ጨርሼ ወደ ስልኬ ሳመራ ድጋሚ መልዕክት ገባ። ከፈትኩት እሱ ነበር። "እንዴት አመሸሽ " ,,,,,,,, " እጆቼ እጆችሽ መንካታቸውን ማመን አልቻልኩም ፣ አይኖችሽን በቅርበት ማየት መቻሌን ማመን አቅቶኛል ከዛም አልፎ ከጎንሽ ተራመድኩ" ይላል መልዕክቱ በስመአብ ሰው በእርጅና ዘመኑ እንዲህ ያብዳል? የ33 አመት ሴት ሳይሆን በውስጤ የምትዘለው ሴት የ16_18 ዓመት ያለች የህፃን ልብ ተሰካ በልቤ ውስጥ ልቤ በደስታ ዘለለ ይሄ ሁሉ አመት በትንሹ ደስ ብለውኝ የሚያውቁ ሰዎች እንጂ እንደዚህ አይነት የሰው መውደድ ደርሶብኝ አያውቅም። መልዕክቱን ለረጅም ሰዓት ስመለከት ቆይቼ መልዕክት ለመመለስ ወደ እራሴ ስመለስ ስጎዬ አሯል ይሸታል ወይኔኔኔኔኔኔኔ ምን ጉድ ነኝ እራሴን እየታዘብኩ ምድጃውን አጥፍቼ ድስቱን አወረድኩት አይጠቅምም ደፋሁት አሁን በድጋሚ ሽንኩርት ከትፌ ስጎ መስራት አለብኝ? ኤጭጭጭጭጭ ምን አይነት ነው ተነጫነጭኩ በራሴ። ትዝ ሲለኝ መልስ አልመለስኩለትም ያው ሴትም አይደለው የተሰማኝን ሁሉ በአንዴ መግለፅ አልፈለኩም እና አጠር ያለች መልስ መለስኩ" ስለተዋወቅን ደስ ብሎኛል" ብዬ መለስኩለት። ወይኔ እኔን ያላየ ከዛ ስጎዬን በድጋሚ ሰራሁ ምስሬን ሰርቼ ጨረስኩ ። የሰራሁበትን አጣጥቤ ቤቴን አስተካክዬ ወደ ፍራሼ ሄድኩ። መልዕክት በድጋሚ መጣ " ተኛሽ አበባዬ" የሚል 😥🙄🥰ልቤ ፈሰሰ መለስኩለት" አይ አልተኛሁም" ብዙ ሀሳብ ወደ ጭንቅላቴ መጣ እራሴን ተቆጣጠርኩ ተቆጣሁ ስልኬን ዘጋሁት ሁኔታዬ አያምርም ። የምሽቱን ፀሎት ፀልዬ ወደ እንቅልፍ ሄድኩ ግን መተኛት አልቻልኩም ስልኬን ከፈትኩት መልዕክት ልኳል። እያወራን ለሊቱን አጋመስን ሳስታውስ ነገ ስራ ገቢ ነኝ በቃ ደህና እደር ጠዋት ስለምነሳ መተኛት አለብኝ አልኩት ሀሳቤን ተቀብሎ መልዕክት መላላክ አቆምን እኔ ግን እንቅልፌ ጠፋ። ጣራ ጣራ እያየሁ መልዕክቶቻችንን ደጋግሜ እያነበብኩ ለሊት 9:15 ሆነ ለመተኛት መታገል ጀመርኩ በስንት ትግል እንቅልፍ ወሰደኝ። ጠዋት12:23 ሲል ነቃሁ እንደረፈደ ተማኝ አዲስ ስራ ጀማሪ አይደለሁ? በፍጥነት ከፍራሼ ተነሳሁ ፊቴን ታጠበብኩ የእለቱን ፀሎት አደረስኩ የተኛሁበትን አስተካከልኩ።ምሳዬን መቋጠር ጀመርኩ እሱን ስጨርስ ወደ ልብሴ ሄድኩ መረጥኩ ያው እንደተለመደው ቆንጆ አለባበሴን ለበስኩ ፀጉሬን አስተካክዬ ሽቶዬን አርከፈከፍኩት ፊቴ ላይ ከውሀ ውጭ የምጠቀመው ተጨማሪ ነገር ስለሌለ ቶሎ እጨርሳለሁ። እራሴን በመስታውት እየተመለከትኩ ተመስገን ይሄን ሞገስ ያላሳጣሀኝ ብዬ ሀብታም መሳይ ድሀ ሆኜ ወጣሁ ምሳ እቃዬን ከጃንጥላ ጋር በትንሽ ማንጠልጠያ ይዤ ስልኬን በእጄ አድርጌ በሬን ቆልፌ ወደ ስራ። ስራዬ ካለሁበት ብዙም አይርቅም የአንድ ታክሲ ጉዞ ነው። የውጭውን በር ከፍቼ ወጣሁ ዘግቼው መንገዴን ጀመርኩ ጥቂት እንደ ተራመድኩ መልዕክት ደረሰኝ ስልኬ እጄ ላይ ስለነበር ከፍቼ አየሁት እሱ ነበር "እንዴት አደርሽ የእኔ ፀሀይ" ኦኦኦኦኦኦኦኦ ወዮዮዮዮ አሰብኩ እያየኝ እንደሆነ ስለዚህ ከፊቴም ከአካሌም የተለየ እንቅስቃሴ ማሳየት አልፈለኩም በውስጤ ግን እየዘለልኩ ነው። መልዕክቱን መለስኩ "እንዴት አደርክ" በነገራችን ላይ እንዴት አደርሽ የእኔ ፀሀይ የሚለው መልዕክቱ ለእኔ ከምኔው ሰማይ እንደደረስኩ ባላውቅም እራሴን ከፀሀይ ውስጥ ፈለኩ እላይ ፀሀይ ላይ የተሰካሁ መሰለኝ ልክ እንደ ፀሀይ የማበራ መሰለኝ። ወይ ጉድ የሴት ችግሯ ይሄ ነው በጆሮዋችን ያኔ ሰይጣን ከገነት ለማባረር የተጠቀመው ቃላቶች ዛሬም በጆሮ ማመኑን ተያይዘነዋል ብቻ የማነበው ወደ ጆሮዬ ስለሆነ የሚሄደው እንደዛ ቀኔን በብርሀን ሞላልኝ። ይሄን ሁሉ እያሰብኩ ሁለተኛ መልዕክት ገባ " ወደ ስራ ነሽ"? አዎ ወደ ስራ ነኝ። የት ነህ አልኩት ? እዚው ነኝ መምጣት እችላለሁ? ሰላም ልበልሽ? አቤት ትህትናውውውውው ይሄማ ሰው የራሱን ቤት ለመግባት እራሱ የሚያስፈቅድ ይመስላል። አዎ ትችላለህ። ባይለኝም እኔ ላየው ፈልጌ ነበር ከማለቴ ዞር ስል አጠገቤ ነው። ተገርሜ የቱጋር ነበርክ አልኩት እዚው አካባቢ አለኝ ሆሆሆሆሆ ከሰማይ የወረደ ነው የሚመስለው እኮ። ሰላምታ ተለዋወጥን እና አብረን መራመድ ጀመርን። እውይይይይ ዝነጣው ሲያምር የእውነት ወንድ በቃ ደሞ ጠረኑ ንፁ ደስ ሲል ብቻ በጣም እኔ የምወደው አለባበስ ለብሷል። ደስ የሚል ሽቶውን አርከፍክፏል። ስንራመድ ምንም አናወራም እኔም በየመሀሉ እየሰረቅኩ እያየሁት አስባለሁ እሱም እንደዛው። ታክሲ የሚዝበት ቦታ አደረሰኝ ደህና ዋል ብዬው ወደ ታክሲ ገባሁ።እሱ ወደ ኋላ ተመለሰ እኔም ወደ ስራ ሄድኩ። ታክሲ ውስጥ ቁጭ ብዬ ስለ እሱ ማሰብ ጀመርኩ ወይኔ ለካ ሴት ፍቅር ሲዛት ጭንቅላቷን ታጣለች የሚባለው እውነት ነው። እንዴ በአንድ ቀን እንዴት ፍቅር ያዘሽ? አትበሉ ልባችንን ነፃ እና ክፍት ካደረግነው የምንፈልገውን ካወቅን በደንብ የፍቅር ስሜት መሰማት ይችላል።እና ከዛ አዲሱ ስራ ቦታዬ ደረስኩ አይገርምም ሰው አያስተውለውም እንጂ የሁሉም ነገር ምላሽ በአንድ ቀን ሊሆን ይችላል ወይም እኛህ አባት የመረቁኝ ምርቃት ከፀሎቴ ጋር ተባብረው ወደ እግዚአብሔር ደርሶ ይሆናል። ለስጋዬ ለኑሮዬ አዲስ ስራ ለልቤ ለመንፈሴ አዲስ የፍቅር እንግዳ ተያይዘው በአንድ ቀን ወደ ቤቴ ገቡ። በጣም ደስ ብሎኛል ለእኔ አለም ዘጠኝ ሳትሆን አስራ አምስት ሆናልኛለች። ስራ ቦታ ደረስኩ ቦርሳዬን ከጠረፔዛ አስቀምጬ ቀና ስል አለቃዬን ፊት ለፊቴ አየሁት። ድንጋጤዬ ወደር አልነበረውም ........ 🙄🙄🙄🙄✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️

✍️✍️✍️መነን ዳንኤል

part 2 የመጀመሪያውን ገፅ ያንብቡ ቀድመው።     ✍️✍️ ስልኬ ጠራ አካባቢዬን በአትኩሮት እየቃኘሁ ወደ ስልኬ ጥሪ ተመለከትኩ፣ የማላውቀው ቁጥር ነበር። አነሳሁት፦ ሄለው ፣ ሄለው፣ እረ...
24/02/2026

part 2 የመጀመሪያውን ገፅ ያንብቡ ቀድመው።
✍️✍️ ስልኬ ጠራ አካባቢዬን በአትኩሮት እየቃኘሁ ወደ ስልኬ ጥሪ ተመለከትኩ፣ የማላውቀው ቁጥር ነበር። አነሳሁት፦ ሄለው ፣ ሄለው፣ እረ ሄለው መልስ የለም ግራ እየተጋባሁ የበሬን ቁልፍ ከቦርሳዬ መፈለግ ጀመርኩ በድጋመመ ጠራ ስልኬ ድምፁን ቀነስኩ እና ቁልፍ መፈለጌን ቀጠልኩ አገኘሁት እና በሬን ከፍቼ ወደ ውስጥ ገባሁ ወረቀቱን በእጄ ይዤዋለሁ ስለ ተላከው መልዕክት ማሰብ ማቆም አልቻልኩም።ልብስ እየቀየርኩ በድጋሚ ስልኬ ጠራ አነሳሁት። ሄለው ..... እረ ሄ..ለው በሶስተኛው በጣም የተቆራረጠ ድምፅ ሰማሁ።ቀጠልኩ እኔ "ሄለው ማን ልበል አልኩ "እኔ ነኝ አለ በፍርሀት የራደ ድምፅ ነው ድጋሚ ከመጠየቄ በፊት አዕምሮዬ መገመት ጀመረ እናም እሱ እንዲሆን ተመኘሁ።እኮ አንተ ማነህ ? እእእእእእእ መልክቱን አየሽው? አዎ አይቼዋለሁ። ስልኩን ጆሮዬ ላይ ዘጋብኝ መልሼ አልደወልኩም በልቡ ያለውን ፍርሀት ማዳመጥ ችያለሁ። ስልኬን አስቀመጥኩ እና ወደ ስራዬ ተመለስኩ ትንሽ እርቦኛል ትንሽ አሰብ አደረኩ እና እግሬንና እጄን ፊቴን መጠብኩ። ቀለል ያለ ቶሎ የሚደርስ ምግብ ሳስብ ሽሮ መጣልኝ። ሽንኩርት አቅርቤ እየላጥኩ ደግሞ ደወለ። እራሴን አረጋጋው በሱ ቦታ ለመሆን ሞከርኩ እና በቀስታ ድምፅ ደህና ነህ አልኩት? አልመለሰልኝም እሰማኝ መሆኑን አረጋገጥኩ እና ጥያቄ መጠየቅ ጀመርኩ። እእእእ የእኔ ወንድም ስምህን ትነግረኝ? አዎ ብሎ ስሙን በፍጥነት ነገረኝ እሺ አሁን ቀስ ብለህ ልትለኝ የፈለከውን ንገረኝ ። እሺ መልሼ ልደውል አለኝ እሺ ግን ደግመህ ስትደውል ተረጋግተህ ደውልልኝ እሺ ሀሳብህን ሰብስበህ። እሺ እንደዛ አደርጋለሁ አለ። ስልኩን ዘጋሁት እና ወደ ስራዬ ተመለስኩ። አይገርምም ጭንቅላቴ ይሄንን ሰው ማሰብ ማቆም አልቻለም። ሽሮዬን እየሰራሁ ብዙ ሀሳብ አሰብኩ አይይገርምም እግዚአብሔር ይሁን ካለው ሁሉም በደቂቃ ውስጥ መቀየር ይችላል። ጠዋት ሳወራባቸው የነበሩት ጉዳዮች እያስታወስኩ ተገረምኩ። ሽሮዬ እስኪደርስ የቡና ሱስ አለብኝ የተፈጨ ቡና ነበር እሱን ከጎን ጣድኩት የመመገቢያ ሳህኔን፣ ሲኒ አቀራረብኩ። ይሄን እያደረኩ ሆዴ ሙርሙር እያደረገኝ ስለነበር ማሰብ አቃተኝ እና ለቡና ያቀረበብኩትን ኩኪስ እየበላሁ ሽሮዬን መጠበቅ ጀመርኩ። በድጋሚ ስልኬ ጠራ። " ሄለው " ሄለው አለኝ ተረጋግቷል ትንሽ ፍርሀት ቢኖረውም ለመጠንከር እየሞከረ እንደሆነ ያስታውቃል ድምፁ። እንዴት ነህ አልኩት በጣም በተረጋጋ እና ፍርሀትን በሚያስወግድ ድምፅ። ደህና ነኝ አለኝ ድምፁ ውስጥ ክብሩ፣ ፍቅሩ፣ የልብ ንፅህናው፣ መሸነፉ፣ ለመገዛት እጅ መስጠቱ ያስታውቃል የሱን ልብ ለማወቅ ድምፁ በቂ ነበር ለእኔ። ለዘመናት ያስቀመጥኩት መስፈርት በድምፁ አገኘሁት መልኩን አላየሁትም ቁመቱን አለካሁትም ግን ልቡ ሁሉንም መስፈረሰት አሟላልኝ። እሱ ደፍሮ ሀሳብ ማንሳት እንደማይችል ስለገባኝ ብዙም ወሬ ሳላበዛ ተገናኝተን ማውራት እንደምንችል ነገርኩት ማመን አቅቶት ነበር። እውነቴን መሆኑን አረጋገጥኩለት። ቀጠሮ ይዘን ስልኩን ዘጋሁት። የፃፈልኝን ወረቀት በድጋሚ እያየሁ ብዙ ሀሳብ ማሰብ ጀመርኩ በድንገት ቡና ሲገነፍል ነቃሁ። ለካ እርቦኝ ነበር እስኪ ምግቤን ልብላ። ምግቤን እየበላሁ ቡና እየጠጣሁ ለካ ለብቻ ምንም አይጣፍጥም ። ብቻ እንዲህ እንዲህ እያልኩ አመሻሽ ሆነ ሰርክ ልካፈል ወደ ቤተክርስቲያን ለመሄድ ነጠላዬን ለብሼ ቤቴን ቆልፌ ወጣሁ የውጭውን በር ዘግቼ መንገዴ ስጀምር ስልኬ ጠራ፦ ስመለከት የእሱ ስልክ ነው። አነሳሁት "ሄለው,,,,,, ሄለው መለሰልኝ ምነው? እረ ምንም አለኝ። ተጠራጠርኩ ሁልጊዜ እንደሚያየኝ ስለነገረኝ። የቱ ጋር ነህ አልኩት ? ደነገጠ ለምን አልሽ አለኝ እያየህኝ እንደሆነ ስለተሰማኝ አልኩት። አልደበቀኝም ከየት መጣ ሳልል ከኋላዬ ስዞር አጠገቤ ነው በጣም ደንግጫለሁ ይሄን ሁሉ አመት ስኖር አይቼው አላውቅም። ጥቁር ነው ቁመቱ ከእኔ አይበልጥም እኩል ነን ፀጉሩን አሳጥሮ ነው የተቆረጠው አይኖቹ ፍርሀት እና ፍቅር ተሞልተዋል። የእውነት ዘልልዬ ባቅፈው ደስ ባለኝ በጣም የሚያሳዝን ፊት ነው ያለው። ተጨባበጥን ወደ ቤተክርስቲያን እየሄድኩ ነው ትሄዳለህ? አዎ እሄዳለሁ። እውይይይይይ ሲያምር እፎይይይይይ የጠዋቱ ምርቃት በደንብ ነው የሰራው። ተገረምኩ ቤተክርስቲያን እስክንደርስ ምንም አላወራንም እኔ ብዙ ነገር ኦያሰብኩ ነበር ብዙ ነገር። ተሳልመን ገባን ለየብቻ ተቀመጥን ጉባኤው አልቆ በሰላም እደሩ ተባለ ፀለይኩ የምር ግን ስለሱ ፀለይኩ አንዳንዴ ህልም የሚመስል በህይወት የማይገኝ የሚመስል። ህልምም ከሆነ አልንቃ እውነትም ከሆነ እንደፈቃድህ ይፅና ብዬ ሎቴን ጨርሼ ተነሳሁ እሱ በርላይ እየጠበቀኝ ነበር አደረሰኝ ሰፈሬ አንድም ነገር አላወራንም ወደ ቤቴ ገባሁ የምሽት ልብሴን ለብሼ ቁጭ ብዬ ስለሁሉም ነገር ማሰብ ጀመርኩ ይሄ በአንድ ቀን እንዴት ሊሆን ቻለ? ደሞ አንድ ጎኔ እግዚአብሔር እንኳን በአንድ ቀን በበደቂቃ ሁሉን ማድረግ እንደሚችል ሳስብ ፈገግ ብይ ተመስገን አልኩ። እና የውሀ አጣጬን አገኘሁት እላችኋለሁ። ያው አላወራንም ግን እንደሚወደኝ ነግሮኛል እኔም ወድጄዋለሁ አሁን ቀጣይ ምን ይሆን የሚፈጠረው????🤴👸????

✍️✍️መነን ዳንኤል

✍️ የዛሬ ባለታሪካችን ድብቅ ልብ የዋህ ፊት ያላት ሚስጥር ስለሆነች ስለ አንድ ብልሀተኛ ሴት ነው። 33 አመቴ ነው ትለናለች። ዛሬ አንድ የስራ ውድድ ነበረብኝ እናም በጠዋት ተነሳሁና ወደ ...
23/02/2026

✍️ የዛሬ ባለታሪካችን ድብቅ ልብ የዋህ ፊት ያላት ሚስጥር ስለሆነች ስለ አንድ ብልሀተኛ ሴት ነው። 33 አመቴ ነው ትለናለች። ዛሬ አንድ የስራ ውድድ ነበረብኝ እናም በጠዋት ተነሳሁና ወደ ቤተክርስቲያን ሄጄ የእለቱን ፀሎት አድርሼ ወደ ቤቴ ተመለስኩ። የቀጠሮ ሰአቴ አስኪደርስ ቤቴን እያስተካከልኩ በመስቀያ ላይ ትላልቅ ካፖርታዎች ተሰቅለዋል ከ4 በላይ ናቸው። በራሴ እየተገረምኩ አሁን አንቺ በክረምት እነዚህን ካፓረርት መልበስሽ እርግጠኛ ነሽ? ባትደርሺስ? አሁን ይሄን የሚፈልግ ስንት ሰው አለ? መኖርሽን ሳታውቂ ልብስ ማጨቅ ምን የሚሉት ነው? እረ እባክሽ አውጥተሽ ለሰው ስጪ ካለሽ ለክረምቱ እግዚአብሔር ካደረሰሽ አንድ ይበቃሻል። እያልኩ ከራሴ ጋር እየተሟገትኩ አንዱ ጎኔ አንዱ ጎኔ ይጠቅምሻል አትስጪ ደሞ በዚህ በጋ ማንም አይፈልግም እያልኩ ሳልወስን ወደ ስራዬ ቀጠልኩ። ብቻዬን ነው የምኖረው አንዳንዴ ደስ ይለኛል ብዙ ጊዜ ግን ይደብረኛል ብቻ መኖሬን። ቤቴን አስተካከልኳት እና ስጨርስ ለባበስኩ። በመስታወት ፊት ቆሜ እራሴን እያስተካከልኩ ለራሴ ጥያቄ ጥያቄ ጠየቅኩት። አሁን 33 አመት ሆኖሻል ልጅ የለሽ እንደው በኖርሽው ዘመን ያፈራሽው ጥሪት የለም። አላገባሽም የምትጓጉይለት ህይወት የለሽም ምንድነው ለመኖርሽ ምክንያት አልኩ በመስታውት ምስሌ ላይ እያፈጠጥኩ። ንገሪኝ ሞተሽ ብታድሪ እንኳን እቤት እሬሳሽ ሲሸት ነው ቤትሽ የሚፈተሸው ምን አለሽ አሁን ለመኖር ምክንት? በአይኖቼ እንባ አቀረርኩ። ከዛ አንገቴን ነቀነቅኩ እና ድጋሚ ሌላኛው ማንነቴ ተነሳ። አዎ ለመኖርሽ ምክንያት አለሽ ለሰው ልጅ ማግባት እና መውለድ ለመኖር ምክንያት ሊሆን አይችልም ያ ብቻ ቢሆን አላማው እግዚአብሔር በእናንተ ህይወት ውስጥ አላማ አለኝ አይልም ነበር። እግዚአብሔር በእኔ ህይወት ውስጥ አላማ አለው።ለራሴ ነገርኩት ነገን አታውቂም ዛሬ በ33 አመትሽ ህይወትሽ ሊያበቃ ይችላል እድሜሽን መቁጠር ሳይሆን ያለብሽ ስራሽን ነው። አጥብቄ ለራሴ ነገርኩት። መልኬን እየተመለከትኩ ከእግዚአብሔርን አመሰገንኩ። ሁል ጊዜ ስዘንጥ በራሴ እስቃለሁ በቦርሳዬም ሆነ በአካውንቴ ብር ሳይኖረኝ ስለብስ የሆነ ድርጅት ባለቤት ነው የምመስለው። 😀😂ሳስቅ በመንገድ ሰው ሲያየኝ የሞላልኝ፣ ችግር ያልነካኝ፣ መኪና ማቆሚያ ላይ መኪና ያቆምኩ ነው የምመስለው።አወይ እቴ አሉ እኔ ግን መናጢጢጢጢጢ ነኝ ሳስቅ ብታዩ ብቻ ከራሴ ጋር እንደዛ ስንጫጫ ቆይቼ ለባብሼ ጨረስኩ። ሽቶዬን አርከፍክፌ ሀብታም መሳይ ድሀ ሆኜ ወጣሁ። በሬን ቆልፌ መንገዴን ቀጠልኩ የግቢውን በር ስከፍት እደጅ ቆመው ስለእግዚአብሔር ብለው እየለመኑ ነው ግራ ገባኝ ቦርሳዬም ውስጥ እዚህ ግባ የሚባል ብር አልያዝኩም እቤትም ምንም አልሰራሁም በሩን በእጄ እንደያዝኩ ትንሽ አሰብ አደረኩእና ፦አባቴ ልብስ ብሰጦት ደስ ይሎታል አልኳቸው? አግኝቼ ነው የእኔ ልጅ አሉኝ። ተመለስኩ እና ጠዋት ለክረምት ካስቀመጥኳቸው ካፓርታዎች አንዱን ወስጄ አለበስኳቸው። መረቁኝ፦ ፀጋ ልበሺ ፣ ከሰው በላይ ያኑርሽ፣ እጅሽ እርጥብ ይሁን፣ ከደጅሽ ሰው ከእጅሽ ገንዘብ አይለቅ፣ ስትታይ ሞገስ አለሽ እግዚአብሔር ሞገሱን አብዝቶ ይጨምርልሽ፣ ያላሰብሽው ሲሳይ ይክበብሽ፣ በፀጋ የተሞላ ትዳር ይስጥሸ ክበሪ ለምልሚ ምርቃቱ ለጉድ ተዠጎደገደ በጣም ደስ አላቸው። ያለኝን ሁሉ ብሰጣቸው ደስታዬ ነው ምርቃታቸው የሚደርስ ነው ደስታቸው የሚጋባ ደስ የሚሉ አባት።በቃ በብዙ በረከት ቀኔን ጀመርኩ የስራ ወድድሩ ቦታ ደረስኩ የሀላፊነት ቦታ ነበር ቦታው እንደ ደረስኩ ትንሽ አርፍጄ ስለነበር እንደ ደረስኩ ወደ መፈተኛ ክፍል ገባሁ ተፈተንኩ ውጤቱም እዛው ነበር ጥቂት ጠብቁ ተባልን። ከተወዳዳሪቹ ጋር ስላመለጠኝ ነገር እያወራን ትንሽ እንደ ቆየን ውጤት ደርሷል አሉን ገባን። የመጀመሪያው መስፈርታቸው እውቀት ነው እኔ ነበርኩ የተመረጥኩት ባለባበስ እና በግርማሞገስ ከእውቀቱ በተጨማሪ ። ወይ ጉድ አንዳንዴ ይጠቅማል። ጠዋት እኚህ አባት የመረቁኝ ደረሰ ብዬ እያመሰገንኳቸው ወደ ቤቴ ተመለስኩ።ስለ ትዳር እያሰብኩ እኔ አሁን ባገባ ጥሩ ሚስት መሆን እችላለሁ? እኔ ሌላሰው ብሆን እና እራሴን ብመለከት እራሴን አገባለሁ? መልሱ ሁለቱም አዎ ነበር። በጣም ጥሩ ሚስት ነኝ።አይገርምም ብዙ የሚፈልጉኝ እኔ የማልፈልጋቸው ለትዳር ጥያቄ ያቀረቡ ሰዎች ሁልጊዜ አንድ ነገር ይነግሩኛል አንቺን የሚያገባ በጣም የታደለ እና እግዚአብሔር የሚወደው ሰው ነው ባልሽ እድለኛ ነው ይሉኛል። ይህ እድለኛ የሆነ ሰው እስካሁን በህይወት አላገኘሁትም እኔ እራሱ ላውቀው ልተዋወቀው ፈልግጌ ነበር አልመጣም። ትንሽ ልወዳቸው ያልኳቸው ሰዎች ፈሩኝ ቁንጅናሽ ያስፈራል አሉኝ እሺ በቃ ብዬ ተውኳቸው የወደዱኝን መውደድ አቃተኝ አሁን ማነው ተጠያቂ? እንደዚህ እንደዚያ እያልኩ እና እያሰብኩ ወደ ቤቴ ደረስኩ በደጄ አንድ መልዕክት ተቀምጧል እንዲ ይላል አንቺ ሳታይኝ እንባዬን አፈሰስኩ፣ አንቺ ሳታይኝ ጠዋትም ማታም አንቺን ተከተልኩ፣ አንቺ ሳታይኝ ለአመታት አፈቀርኩሽ ዛሬም ሳታይኝ ፍቅሬን ገለፅኩልሽ። ስምሽን ለመጥራት አንደበት ይንቀጠቀጣል እዶቼ ድፍረት የላቸውም አሁን የምፈልገው አንቺን ለማግባት ንግስቴ ለማድረግ ጊዜው ረፍዶ ይሆናል። ግን እልሻለሁ ዘመኔን ሙሉ እጠብቅሻለሁ። ይላል ግራ ተጋበባው ስም የለው ስልክ ቁጥር የለው ፅሁፍ ብቻ። ነፍሴ ተጨነቀች። ምንድነው የማደርገው? ማነው ይሄ ሰው? ህይወት እንዴት ግራ ነው። የወንድ ሀያቴ ሁሌ እንዲህ ይለኝ ነበር በፊትሽ የሴት ልጅ ርህራሄ ይታያል በሳቅሽ ብልሀትሽ ይታያል ፣ የተቆጠበ ነው፣ በእርምጃሽ እርጋታሽ ይለካል፣ በአንደበትሽ የቃልሽን ውበት እና ማስተዋልሽ ይታያል፣ በዝምታሽ የሚስትነት ትህትናሽ ይታያል፣ በመንገድሽ የእግዚአብሔርን መንገድ መጓዝሽ ያሳያል። ይለኝ ነበር ታዲያ ይሄ ሰው የቱ ታይቶት ይሆን በዚህ ልክ የወደደኝ? ብዬ እየተብሰለሰልኩ ስልኬ ጠራ፦፦፦፦፦✍️✍️✍️✍️

✍️✍️  አንድ ሰው እንዲህ አለ" ድሮ ድሮ ሰዎች እንዳይለዩኝ እፈራ ነበር አሁን ግን ጊዜ እንዳይለየኝ እፈራለሁ"።አለ አይገርምም በኖርነው ልክ ለውጣችን ኑረታችንን ይመስላል ቃላቶቻችን ይለ...
17/02/2026

✍️✍️ አንድ ሰው እንዲህ አለ" ድሮ ድሮ ሰዎች እንዳይለዩኝ እፈራ ነበር አሁን ግን ጊዜ እንዳይለየኝ እፈራለሁ"።አለ አይገርምም በኖርነው ልክ ለውጣችን ኑረታችንን ይመስላል ቃላቶቻችን ይለወጣሉ።ፍርሀት ፍላጎታችን ይለወጣል። በዚህች ለነፍስ ጥጋብ ለስጋ ርሀብ በሆነው ባጭሩ ጊዜ የቱን ፍላጎት እና መንገድ ለመቀየር ተዘጋጀን? ካለፈውስ ምን ለውጥ አለን? ትላንት እና ዛሬ ላይ በማንነታችን ላይ ለውጥ ከሌለ እየኖርን አይደለም ።የሚኖር ሰው የጊዜ ለውጥ ሰዎችን በጥሩም በመጥፎም ይለውጣል። እስኪ እራሳችንን እንፈትሽ።

✍️ ሰላም ጤና ይስጥልኝ የተከበራቹ። ዛሬ በአንድ ታሪክወደ እናንተ መጣሁ። ታሪኩ እውነተኛ ታሪክ ነው። በአንድ ሀገር አንድ ባለፀጋ ነበር። ይሄ ባለፀጋ በጣም የምትወደድ፣ የምትከበር፣ ለሁሉ...
31/01/2026

✍️ ሰላም ጤና ይስጥልኝ የተከበራቹ። ዛሬ በአንድ ታሪክወደ እናንተ መጣሁ። ታሪኩ እውነተኛ ታሪክ ነው። በአንድ ሀገር አንድ ባለፀጋ ነበር። ይሄ ባለፀጋ በጣም የምትወደድ፣ የምትከበር፣ ለሁሉም እናት፣ ማረፊያ፣ ሰው አክባሪ፣ እጅግ በጣም አስደናቂ ሚስት ነበረችው። ልጆቿን አንድም ቀን ከባድ ቁጣም ሆነ ምትበብለ አስተናግደው አያውቁም ልጆቿን የምትቀጣው በዐይኖቿ ብቻ ነበር። ልጆቿ እጅግ የተባረኩ ነበሩ ሀገር ምድሩ የመሰከረላቸው የእኔም ልጆች እንደእነሱ በሆኑ ብለው ሌሎች ወላጆች የሚመኟቸው ልጆች ነበሩ። ሰው የሚያከብሩ፣ እናት አባታቸውን የሚያከብሩ፣ ስርአት ያላቸው ልጆች ነበሩ።ይህቺ የባለፀጋ ሚስት ለሁሉም እናት ነበረች። ጀግናም ሴት ነበረች። በቤቷ የወንድ እና የሴት ሰራተኞች ነበራት። ለሰራተኞቿ አሰሪ ወይም አለቃ ሳትሆን እናት ነበረች እሷ ቤት ለሰራተኝነት የገባ ወንድም ሴትም ቢሆን ያላገባ ከሆነ ድራ ሞሽራ ጎጆ የምታወጣ ካገቡ ቤተሰባቸውን ቤተሰቧ አድርጋ የምትኖር ድንቅ ሴት ነበረች። ታዲያ ከእለታት በአንዱ ቀን የባለፀጋው ሚስት ወደ ገበያ ትሄዳለች፣ የደረሱት ልጆቿ ወደ ትምህርት ቤት ህፃናቱም ወደ ጨዋታ ይሄዳሉ በዚህን ጊዜ በሰፈሩ ማንም እንደሌለ ያጣራው የቤቱ አገልጋይ፤ የቤት ሰራተኛዋን ይደፍራታል። ብትጮህ፣ ብታለቅስ፣ ብትለምነው፣ ሊሰማት አልወደደም እናም ክብረ ንፅህናዋን ባሰቃቂ ሁኔታ የወስዳል ያለፍላጎቷ አስገድዶ ይደፍራታል። ይህ ከሆነ ከሰዓታት በኋላ የቤት እመቤቷ ስትመለስ ከገበያ ያየችውን ማመን አቃታት ፣ የተደፈረችው አገልጋይ ደፍራት ባለችበት ጥሏት ስለሄደ እግሮቿን በመሸማቀቅ አጣጥፋ ከነ ደሟ ባለችበት እያለቀሰች ነበር። ስታያት ድንጋጤዋን መቆጣጠር አልቻለችም። የተፈጠረውን እንድታስረዳት ጠየቀቻት። አገልጋይዋ ቃላት ከአንደበቷ አጣች ህመሟን ስቃይዋን የሚገልፅ ቃል አጣች እናም ማልቀሷን ቀጠለች። እመቤቲቷ በብዙ ማባበል እና ማዘን በኋላ የተፈጠረውን አወቀች ። ደነገጠች እንደ ልጅ የምታስበው ወጣት ነበር ይሄን ጥቃት የፈፀመው ንዴቷን መቆጣጠር አቃታት። ባለቤቷ እስኪመጣ ከደጅ ቁጭ ብላ ጠበቀችው።ልጅቷን ማስተካከል አልፈለገችም ፅኑ ወሳኔ እንዲወሰንበት ፈልጋ ሰስለነበር። አመሻሽ ባሏ መጣ። የሆነውን ሁሉ ልጅቷን በአይኑ እንዲያይ እያደረገች ነገረችው። ደነገጠ።ትዕዛዝ አስተላለፈ ሰራተኛው እንዲጠራ፤ አልነበረም ።ልጅቷን ማጣጠብ ጀመረች ልብሷን ቀየረችላት እንድታርፍ ወደማረፊያዋ ወሰደቻት። ከባሏ ጋር ማውራት ጀመረች ይሄ ሰው ወደ ህግ ልንወስደው ይገባል አለችው። መልስ አልሰጣትም እየተናደደች መጣች እሺ መፍትሄው ምንድነው ስትል ጠየቀችው አሁንም በዝምታ አለፋት። አንድ ውሳኔ አሳወቀችው ይሄ ሰው ለህግ ካላቀረብከው እኔ እና ሴት ልጆቼ ከዚህ መራቅ ይኖርብናል።የተጠቃችውንም ጨምሬ ከዚህ መራቅ ይኖርብናል ነገ ልጆቼ እና እኔ ላይ ጥቃት አለማድረሱ ምንም ዋስትና የለንም። የተጠቃችውም ልጅ ልጄ ናት አንተ ካልተከላከልክላት እኔ አደርገዋለሁ። ብላ ወደ መኝታ ክፍሏ ገባች። ባሏ ሲያስብ እና ያንን ጥቃት የፈፀመውን ሰራተኛ ሲጠብቅ ለሊቱ ተጋመሰ። እሷም በአይኗ እንቅልፍ ሳይዞር ለሊቱ ነጋ። በማለዳ ተነሳች ሰራተኛው ከባለቤቷ ጋር ግቢ ውስጥ ቆመው ሲነጋገሩ አየች ደሟ ተንተከተከ ሰውነቷ ተንቀጠቀጠ የሆነ ነገር ብታደርገው በወደደች ግን ባሏን ስለምታከብር ውሳኔውን ለእሱ ሰጠች። ከባለቤቷ ጋር ተነጋግረው ሲጨርሱ ወደ እሷ መጡ ልጅቷን ጠርተው ለመነጋገር ይመስላል እመቤቲቱ ግን አይኑን ማየት እንኳን ስላልፈለገች ጥለቸው ሄደች። ልጅቷ ተጠራች የተወሰነ የማያስማማ ሀሳብ አንስተው ሊያስሟሟት ሲክሩ ደረሰች እመቤቲቱ። አይሆንም አለች እኔ እሱን በህግ መጠየቅ እፈልጋለሁ አለች ባለቤቷ ግን ጉዳዩ ከቤት እንዳይወጣ ውሳኔ አስተላለፈ። እመቤቲቱ ቁጣዋ ከባድ ነበር እንደዚህ አይነት ጥቃት ያንገበግባታል ተጠቂዋንና አንድ የደረሰች ሴት ልጇን ይዛ ወደ ቤተሰቦቿ ሄደች። ባሏ ደነገጠ ከ3 ቀናት በኋላ ሽማግሌ ልኮ ወደቤት እንድትመለስ ጠየቃት። እሷም ይሄ ጥቃት በህግ ከተጠየቀ ብቻ እመለሳለሁ አለች። ሽማግሌዎቹም አስተባበሉ አግባቡዋት በሀገሩ ባህል ህግ ጋር ሳይደርስ በሽማግሌ ያልቃል ተባለች። የሀገር ሽማግሌዋች ስለነበሩ ሀሳባቸው በብዙ አሳምኗት ልጇንና ተጠቂዋን ይዛ ወደ ቤት ተመለሰች። ሽማግሌዋቹም እንደተባባሉት ነገሩን ያዙ። ለልጁ ሁሉም ነገር አሟልቶ እንዲያገባት ፈረዱበት ይሄ ሂደት ተንጓቶ ስለነበር ከ3 በኋላ ማርገዟን አወቀች የሽማግሌዋቹ ሀሳብ ተቀበለ አሁን በእጄ ላይ ምንም ገንዘብ የለም የተወሰነ ጊዜ ትጠብቀኝ የተባለውን ሁሉ አደርጋለሁ አለ። ሽማግሌዎቹም እንድትጠብቀው አስሟሟቸው። ወደቤት ተመልሰው እዛው ቤት መኖር ጀመሩ።የመውለጃዋ ጊዜ ደረሰ እሱም ምንም ሳያደርግላት ወለደች። አሁንም እመቤቲቱ ሀሳብ ማንሳት አላቆመችም። ተጋብተው ጎጆ እንዲወጡ የታዘዘውን ሁሉ እንዲያደርግላት ሁሌም ታስታውሰዋለች። በመሀል እመቤቲቱ ታመመች ከጥቂት ወራት በኋላ ሞተች። ያቺም ተጠቂ ሳያገባት የተባለውም ሳያደርግላት በድጋሚ አረገዘች። ሁለተኛውን ልጅ ወለደች። ሁለተኛውን ልጅ በወለደች በ 3ኛው ወር ሰፈር ውስጥ የነበረች ልጃገረድ ጠልፎ ወደ አዲስ አበባ ተሸሸገ ለ ሁለት አመት ከቆየ በኋላ ለባለ ፀጋው ሽምግልና እንዲሄድለት ጠየቀው ለጠለፋት ልጅ ቤተሰቦች። ሄደለት እነሱም ምርጫ አልነበራቸውም ሽምግልናውን ተቀበሉ ምክንያቱም ልጃቸው ካስወለዳት በኋላ ነበር ሽምግልና የላከው።ተጠቂዋ ሁለት ልጆችን ብቻዋ እንድታሳድግ ተፈረደባት እሱ ደሞ በድጋሚ ጥቃት ፈፅሞ አዲስ ህይወት እንዲኖር ተፈቀደለት። አለም እንደዚህ ናት። ሴት ልጅ ጥቃቷ ህመሟ ማንም ልብ ውስጥ የለም ። በጣም የሚያም ህይወቶች አሉ የሴት ልጅ ትላንት ችግር የለውም ብሎ ዛሬን የሚያክም ከጥቃት የሚጠብቅ ማህበረሰብም ሆነ ህግ ያለ አይመስለኝም። ወንድ ልጅ ትላንቱ ምንም ቢሆን አዲስ ነገር ይፈልጋል። እናም ያገኛል የማይፋቀው የሴት ትላንት እንጂ የወንድ ትላንት አይደለም። ይገርመኛል ይሄ ሀሳብ በሰው ጭንቅላት እንጂ በእግዚአብሔር አይን ሁሌም በንስሀ ስንታጠብ የማይፋቅ የማይሻር ህመምም ትላንትም የለም። እኔ ለሁሉም መፍትሄው ሰዎች ለሚያዩት ማንነት ሳይሆን እግዚአብሔር ለሚያየው ማንነታችን እንትጋ። ይሄ ህመም ያለበት ብዙ ቦታ ይኖራል በቃ አሁን እራስን ለእግዚአብሔር ሰጥቶ መንፃት አለ እና ሰዎች በትላንት ጥቃት እና ወድቀት በትላንት ማንነት ቢጠሯቹ አቤት አትበሉ የስጋ ቁስል አይለም የነፍስን ቁስል የሚያክም እግዚአብሔር ያዙ።እሱ አዲሱ ስማቹ ይሁን። ሁሌም አዲስ የሚያደርገው እርሱ ስለሆነ። ክብር ለመድሀኒያለም ይሁን።

✍️✍️ሰላም የተወደዳቹ፦ ዛሬ አንድ ያስደነቀኝን ሀሳብ ላካፍላቹ። በባለፈው እሁድ የቤተሰብ ሰርግ ነበረብን። እናም ሰርጉ በቤተክርስቲያን ስርአት ነበር የተፈፀመው።ሰርገኞቹን አጅበን ከቤተክር...
30/01/2026

✍️✍️ሰላም የተወደዳቹ፦ ዛሬ አንድ ያስደነቀኝን ሀሳብ ላካፍላቹ። በባለፈው እሁድ የቤተሰብ ሰርግ ነበረብን። እናም ሰርጉ በቤተክርስቲያን ስርአት ነበር የተፈፀመው።ሰርገኞቹን አጅበን ከቤተክርስቲያን ወደ ቤት ይዘን ተመለስን የሚያርፉበት አዳራሽ ካስገባን በኋላ ከድንኳኑ ትንሽ ፈንጠር ብለን ቁጭ አልን።ከታላቅ ወንድሜ ጋር ነበርኩ። የሆነ ሀሳብ አንስተን እየተወያየን እያለ ድንገት ከፊታችን በአካባቢው የተከበረ ባለፀጋ ሰው ከሚስቱ ጋር አለፉ። ወንድሜ እንዴት አንዳያት አላውቅም ግን የባለፀጋው ሚስት ጫማ ልክ አልነበረም። እናም አንገቱን እየነቀነቀ ምናለ ጫማዋን ቢያስተካክልላት አለ።ስላላየኋት ምን ሆኗል ጫማዋ?። ብዬ ጠየቅኩት። ስመለከት ጥሩ የሚባል አለባበስ ነው የለበሰት። እና ግራ ገባኝ። ልክ አይደለም አለኝ። እንዴት? ባይሆንስ እሷ ጫማዋን እንዴት አትመለከትም ለአለባበሷ የሚሆን ጫማ እንዴት አትመርጥም? የሚል ጥያቄ አቀረብኩለት። እሱም እንዲህ ሲል መለሰልኝ።' አየሽ ሴት ሁሌም መጠበቅ ትፈልጋለች።ከሞቀ ህይወቷ የወሰዳት እኮ ሊንከባከባት ሊጠብቃት እንዲሁም ሌላ እንጂ የራሷ ጉዳይ ብሎ ሊተዋት አይደለም። እእስኪ አስቢው በእናትሽ ቤት ስትኖሪ መጎሳቆልሽን አይታ የምታስተካክልሽ እናት ወይ አባት አለሽ አይደል። ብትጎሳቆይ ሰው አንቺን ሲያይ የገሌ ቤት ምን ሆነዋል ብሎ ይጠይቃል። መጎሳቆልሽ የቤተሰብሽን ሁኔታ ስለሚያሳይ። ስታገቢም እንደዛው። የእገሌ ሚስት ምን ሆናለች፣ የወንዱም እንዳለ ሆኖ የሴቶች ይጎላል። ስለዚህ አንድ ወንድ የሚስቱን ሁኔታ በጣም መከታተል መንከባከብ ግዴታው ነው በሷ ማማር መዋብ የሚጠራው እሱ ስለሆነ። አንድ ነገር ልንገርሽ ሴት ልጅ ባለቀለት ህይወት መምጣት እንዳለባት የቀደመው አዳም ለዚህ ምሳሌ ነው እግዚአብሔር ሁሉን ካስተካከለ በኋላ ነው ሄዋንን የፈጠረለት። ሴት መከበሪያሽ ነች። የበሰለ ወንድ ሁሌም ሚስቱን ሲንከባከብ እና ሲያከብር ታይዋለሽ። ሴት የሰጠሻትን ነው የምትመስለው። የምትሰጠውም በዛ ልክ ነው። አሁን ይሄን ሁሉ ያነሳሁት በእነዛ ሰዋች ነው እሱ የእኛ ቤተሰብ ነው እና ቤተሰቡ ጋር ይዟት ሲቀርብ ሁሉ ነገሯን መመልከት እና ማየት አለበት እንኳን የእሱ ቤተሰብ ጋር የራሷ ቤተሰብ ጋር ስትሄድ ሊጠነቀቅላት ሊያስተካክላት ግድ ይለወዋል። ከቤተሰሰቧ ሲቀበላት ሊንከባከባት እና ሊጠብቃት እስከወሰዳት ድረስ ግዴታው ነው። ለሱም መከበሪያዎ ነች። አለኝ እና በጣም አስደንቆኛል ሁሌም ስናወራ አስተሳሰቡ ይደንቀኛል እናም ወንዶችን በእሱ ምሳሌ ባደርግ ሁላ ደስ ይለኛል። የእሱ ሚስት እንዴት እንደፀለየች ባላውቅም ትክክለኛ ባል አግኝታለች። የእኔ ውድ ወንድም መካሪዬ ጓደኛዬ ህይወትህን ሙሉ እግዚአብሔር ይባርክልህ ቤተሰብህን ይጠብቅልህ።

ሰላም እንዴት ከርማችኋል። ጠፍቻለሁ አይደል የሚነገር ታሪክ ጠፍቶ ሳይሆን አንገብጋቢ ስላልነበሩ ነው። ዛሬ ወደ እናንተ ያመጣኝን አንድ ታሪክ ላካፍላቹ ትማሩበታላቹ እንዲሁም እራሳቹን ታዩበታ...
29/01/2026

ሰላም እንዴት ከርማችኋል። ጠፍቻለሁ አይደል የሚነገር ታሪክ ጠፍቶ ሳይሆን አንገብጋቢ ስላልነበሩ ነው። ዛሬ ወደ እናንተ ያመጣኝን አንድ ታሪክ ላካፍላቹ ትማሩበታላቹ እንዲሁም እራሳቹን ታዩበታላቹ።
✍️✍️ አንዲት ቅን ልብ ያላት እንስት ዛሬ አስተርዮም ማሪያምን ለማክበር ስሄድ ተዋወቅኩ።እንኳን አደረሳቹ። እናም ከጎኔ ተንበርክካ እየፀለየች ነው ፀሎቷ ለእኔም ይሰማል፣ ሳታስበው ድምጿን ከፍ አድርጋ ከአምላኳ ጋር እየተነጋገረች ነው። ባልሰማ እመርጥ ነበር ግን አልቻልኩም። ፀሎቷን ጨርሳ ስትነሳ አይኖቿ ቀልተዋል፣ ፊቷም እንደዛው። ግን የሆነ ሰላም ፊቷ ላይ ይታያል።በእጄ ጠዋፍ ይዤ እያበራሁ ነበር ፣ ለመለኮስ እጆቿን ወደ ያዝኩት ጠዋፍ ሰደደች አብርታም ከአንከቷ ዘንበል ብላ ወደ ቤተመቅደሱ መመልከት ጀመረች ።አይኖቼን ከእሷ ላይ መንቀል አልቻልኩም። ቆንጆ ናት ቀይ ።፣ፀጉራ በሻሽ ተሸፍኗል፣ ባቷ በሰፊ ሽፎን ሸፍናዋለች፣ በስርዓት ያደገች ትመስላለች።እድሜዋ ወደ 32 አካባቢ የምትሆን ትመስላለች ጭምት ያለች ነች።በጣቶቿ ቀለበት የለም። አለማግባቷ በፀሎቷ ሰምቻለሁ እግዚአብሔርን እንደ ቅርብ ተጠሪዋ እንደ ጓደኛዋ የምታወራው ትመስላለች ልክ እንደ ልጅ እና አባት፣ እሱም መልሱን ያዘገየባት የእኔ ናት አኩርፋ ሌላ ቦታ አትሄድም ጠብቂኝ የሌሎቹን እስክጨርስ ያንቺ በልዩ ሁኔታ ነው የምሰራልሽ የሚል ይመስላል። ከፀሎቷ ስረዳ ለረጅም ጊዜ ያልተመለሰ ጥያቄ እንዳለ ነው።እናም መጠየቅ ፈለኩ በሰአቱ ማውራት ስለማንችል መጠበቅ ነበረብኝ።ሰዓቱ ሲደርስ እራሷ አወራችኝ በፊታችን ልጅ ይዘው የሚያልፉ ጥንዶችን አየች እና ዞር ብላ፥ አያምሩም? አለችኝ 'ያምራሉ አልኳት።
በምድር ላይ ትልቁ በረከት ነው ለልጅ የሚከፈል መስዋትነት በረከት ነው።እግዚአብሔር ልጅ ሲሰጥ ሲተማመንብሽ እና ሲባርክሽ ነው አለች። ግን እኮ እግዚአብሔር በብዙ ነገር ይባርካል አይደል እንዴ? ብዬ ጥያቄ አስከተልኩ። አዎ እሱ ልክ ነሽ ግን እኔ ልጅ ድክመቴ ነው አለችኝ። ይሄን ተጠቅሜ ስለሷ ማወቅ ፈለኩ። ስሜን ነገርኳት፥ ስሟን ነገረችኝ። አግብተሻል አለችኝ የእኔን ሳልመልስ የሷን ጠየቅኳት አላገባሁም አለችኝ። ታሪኬ ብዙ ነው አለችኝ። ጓጉቼ ስለነበር ፤ ትንሽ መስማት እችላለሁ ከታሪክሽ አልኳት። አንገቷን በአዎንታ እየነቀነቀች እሺ አለችኝ። ለመስማት እራሴን አዘጋጀሁ። ትነግረኝ ። ታሪኳ የሚጀምረው ከ 14 አመቷ ነው በ14 አመቷ እናቷ ሞተች እናም እቤት ውስጥ ታናናሾቿን የመጠበቅ፣ ቤት ውስጥ ሁሉም ሀላፊነት የእሷ ነበር ።ትምህርት ፣የቤት ሙሉ ሀላፊነት ቀጠለ አባቷ ሚስት አገባ ይሄኔ የቤት ሀላፊነት ቀለልኝ ስትል ሌላ ተጨማሪ ችግር አባቷ የምትማርበትም ሆነ የትኛውንም ወጪ አልሰጥም አለ። እንደምንም ተማሙታ ለትምህርት ወደ ከተማ ሄደች የተወሰነ ወጪዎቿን ትምህርት እየተማረች ከጎን ስራ ጀመረች ትህርቷን 12 ከጨረሰች በኋላ ጥሩ ውጤት አመጣች ግን university መግባት ፈራች ማን ያግዘኛል ብላ ተጨነቀች የነበራት አማራጭ ኮሌጅ መግባት ነበር።እየተማረች መስራት የምችለው እዚህ ነው ብላ ስላመነች። ከዛም ትምህርቷን ቀጠለች 2 አመት የኮሌጅ ተማሪ ሆና አፈቀርኩሽ የሚል መልዕክት በተደጋጋሚ ይደርሳታል። ብዙ ይደርሷታል። የእሱ ተለየ መሞቴ ነው አንቺን ካላገኘሁ አለ በስራ ቦታዋም በትምህርት ቤትም ማፍቀሩን አስመሰከረ። ሰው ሁሉ ለምን እሺ አትይውም የሚል ጭቅጭቅ ሰላሟን ነሳት።ሴት የሚወዳትን እንጂ የምትወደወን ማግባት የለባትም።የሚያከብርሽ፣ የሚኮራብሽ፣ ያንቺ ህይወት እና መንገድ የሚያስጨንቀው፣የሚንከባከብሽ፣ የሚታመንልሽ።ተዘርዝሮ የማያልቅ ሀሳብ ተሰጠኝ እና ማሰብ አቆምኩ። እኔ ነኝ እነሱ ናቸው ትክክል ብዬ መወዛገብ ጀመርኩ። ይሄ ሁሉ ሰው እሱን ለእኔ ከመረጠልኝ እኔ እሱን ያለመፈለጌ ስህተት ነው።ብዬ አመንኩ እናም በሰው ሀሳብ ህይወት ለመጀመር ወሰንኩ።
በእርግጥ መጥፎ ሰው አልነበረም ግን ምቾት የነሳኝ ነገሮች ነበሩት። ወስኜ አብሬ ከሆንኩ በኋላ ወደኋላ መመለስ አልፈለኩም ላስተካክለው በጣም ሞከርኩ።ሁሌም ከእሱ ጋር ሆኜ ብቻዬ ነበርኩ። ሲያቅድ በህልሙ ውስጥ አልነበርኩም ፣የወደፊት ህይወቱ ውስጥ አልነበርኩም፣ ከስኬቱ መሀል እኔ ከጎኑ የለሁም።ወደፊት በሚኖረው ሁሉ ውስጥ የለሁም።ስለዚህ ብቻዬን ነበርኩ። ይሄንን ለመቀየር ሞከርኩ የማይሆን ሆነብኝ። ስለእኔ ነገ ምንም ግድ ሳይሰጠው በየትኛውም ነገር ሊቆጣጠረኝ ሞከረ። ከመጠን በላይ መቅናት፣ በየጊዜው መጣላት። ይሄ እየበረታ ሲመጣና ከዚህ የባሱ ነገሮች እያጋጠሙን ሲመጣ እኔ ብቻዬን ማስተካከል እንደማልችል ሲገባኝ ጊዜውን በዝምታ አሳለፍነው ።እናም እኔ ወስኜ ወጣሁ።ለመመለስ ሞክክሮ ነበር ፣ እራሴን አጠፋለሁ ብዙ ዛቻ ደረሰብኝ።ይሄን ሁሉ ለማምለጥ ትምህርቴን እንደጨረስኩ ስደትን ምርጫዬ አደረኩ።ይቀጥላል

Address

28-78031
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Menen Daniel posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share